በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በጥቁር ልብስ ምክኒያት ከሥራ የታገዱ ሰዎችን ጉዳይ የቤተክርስቲያኒቷ ሕግ ቡድን እየተከታተለው ነው


በጥቁር ልብስ ምክኒያት ከሥራ የታገዱ ሰዎችን ጉዳይ የቤተክርስቲያኒቷ ሕግ ቡድን እየተከታተለው ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:47 0:00

በኢትዮጵያ ኦርቶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተፈጥሮ ከነበረው ችግር ጋራ በተያያዘ ከሥራ የታገዱ ሠራተኞችን ጉዳይ እየተከታተለ እንደሚገኝ የቤተክርስቲያኗ የሕግ ቡድን አስታወቀ።

ከታገዱ ሠራተኞች መካከል አስተያየታቸውን ለአሜሪካ ድምጽ የሰጡ አንዲት ግለሰብ፣ መፍትሔ ካላገኙ ቤተሰባቸው ለችግር እንደሚጋለጥባቸው ተናግረዋል፡፡

የቤተክርስቲያኗ የሕግ ቡድን አባል ዲያቆን ዘካሪያስ ወዳጅ፣ በሥራቸው ላይ ችግር የተፈጠረባቸውን ሰዎች እያገኙ በማናገር ላይ መሆናቸውንና ችግሩ በአስተዳደራዊ መንገድ ካልተፈታ ወደ ሕግ እንደሚወስዱት ለአሜሪካ ድምጽ ገልጸዋል፡፡

በተያያዘ ዜና፣ ፖሊስ ሕገመንግስታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ ኅብረተሰቡን ለሽብር በማነሳሳት ወንጀል ጠርጥሪያቸዋለሁ ያላቸውን መምህር ምህረተአብ እና ወ/ሪት ፌቨንን ጨምሮ በእነርሱ መዝገብ ስር የነበሩ ሌሎች ሦስት ተጠርጣሪዎችን ከእሰስር መልቀቁም ታውቋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG