በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሳይንሳዊ ምርምር ጥናት ባለቤት የ15 ዓመቷ ክርስቲያን ተኮላ


የሳይንሳዊ ምርምር ጥናት ባለቤት የ15 ዓመቷ ክርስቲያን ተኮላ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:45 0:00

የሳይንሳዊ ምርምር ጥናት ባለቤት የ15 ዓመቷ ክርስቲያን ተኮላ

በዩናይትድ ስቴትስ ቨርጂኒያ የምትኖረው የ10ኛ ክፍል ተማሪ እና የ15 ዓመቷ ትውልደ ኢትዮጵያ ክርስቲያን ደረጀ ተኮላ የሳይንሳዊ ግኝት ሆኖ የተመዘገበው ጥናታዊ ሥራ ባለቤት ሆናለች፡፡

ጥናታዊ ሥራው “የተለያዩ ማጽጃዎች በፍሪጅ መደርደሪያዎች ላይ ባሉ ባክቴሪያዎች እድገት የሚያሳድሩት ተጽእኖ Effects of Cleaning Agents on Bacterial Growth in Refrigerator Surfaces “በሚል ርዕስ የታተመ የምርምር ጽሁፍ ነው።

የክርስቲያን ተኮላ ስራ ለህትመት የበቃው በሃርቫርድ እና ጆን ሀፒክንስ ዩኒቨርስቲ ከሚገኙ ሁለት ተባባሪዎችዋ ጋር ነው፡፡

ጽሁፉን ያተመው ደግሞ በመላው ዩናይትድ ስቴትስ ባሉ ተመራቂ ተማሪዎች እና ድህረ ምረቃ (ዶክተር) ተማራማሪዎች እንዲሁም ፕሮፌሰሮች አጋዥነት የሚታተመው The Journal of Emerging Investigators (JEI) የአካዳሚ መጽሄት ነው፡፡

XS
SM
MD
LG