በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አይ ኤስ የሽብር ቡድን በፓኪስታን ከፍተኛ ዲፕሎማት ላይ አፍጋኒስታን ውስጥ ጥቃት አደረሰ


በካቡል የሚገኘው የፓኪስታን ኤምባሲ ደጃፍ ላይ የጸጥታ አካላት ቆመው
በካቡል የሚገኘው የፓኪስታን ኤምባሲ ደጃፍ ላይ የጸጥታ አካላት ቆመው

ዩናይትድ ስቴትስ ታሊባን ፓኪስታን ውስጥ የሽብረተኛ ቡድኖች በመዋጋት በኩል ተገቢውን ስራ እየሰሩ አይደለም በሚል ስጋቷን እየገለጸች ባለችበት በአሁኑ ሰዓት ቅዳሜ ዕለት አፍጋኒስታን ውስጥ ለተገደሉት ፓኪስታናዊ ዲፕሎማት የግድያ ሙከራ ሃላፊነቱን እንደሚወስድ እስላማዊ መንግስት በመባል የሚታወቀው የሽብር ቡድን ገለጸ።

የአፍጋኒስታን ባለስልጣናት የፓኪስታኑ ቆንስላ ኡበይድ-ኡር-ረህማን ኒዛማኒ ካቡል በሚገኘው ኤምባሲ ቅጽር ግቢ ውስጥ የተለመደ የከሰዓት የእግር ጉዟቸውን ሲያደርጉ ሳሉ በአቅራቢያ ካለ ህንጻ ላይ ተኩስ እንደተከፈተባቸው አስታውቀዋል።

ይህን ተከትሎም እሳቸው ምንም ሳይደርስባቸው ቢያመልጡም የደህነነት ተባቂያቸው ግን ደረቱን እና እግሮቹን በጥይት መመታቱ ታውቋል።

ፓኪስታን ጥቃቱን ያወገዘች ሲሆን ታሊባን አጥቂዎቹን ለህግ እንዲያቀርብ እና በአፍጋኒስታን ለሚገኘው ልዑኳ የሚያደርገውን የደህንነት ጥበቃ እንዲያጠናክር ጠይቃለች።

እሁድ ዕለት የፓኪስታን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከታሊባን ባለስልጣናት ጋር የአይኤስ አይኤስ-ኬ ያልተሳካ የግድያ ሙከራን በተመለከተ “በገለልተኝነት እና በመመካከር” ለማጣራት እየሞከረ እንደሚገኝ አስታውቋል።

XS
SM
MD
LG