ዋሽንግተን ዲሲ —
“ ይማሩ ” በመላ ዓለም ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የእንግሊዝኛ ክህሎትን የሚያስተምር የዮቲዩብ አምድ (ቻናል ) ነው። ከ160ሺ በላይ ተከታዮች ያሉት አምዱ ፣ ወደ 90 የሚጠጉ በጥሩ ጥራት የተቀናበሩ ማስተማሪያ ምስሎችን አካቷል። በወጣቶች የተመሰረው “ይማሩ” ቀለል ባለ አቀራረብ የእንግሊዝኛ ንግግርን ለማሻሻል ይረዳሉ ያላቸውን ሀሳቦች በማቀበል ላይ ይገኛል።
ሀብታሙ ስዩም ከአምዱን መስራች አማኑኤል እስራኤል እና “ በይማሩ” አውታር ላይ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መምህርት ከሆነችው በጸጋ ጌታቸው ጋር በማህበራዊ መገናኛ በኩል አጭር ቆይታ አድረጓል። መልካም ቆይታ ።