No media source currently available
የቴሌቭዥን መስኮት ለሚያዘወትር ሰው ማርታ ኃይለየሱስ እንግዳ አትሆንበትም። ደርሶ -መልስ በተሰኘው ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ ላይ በነበራት የትወና ተሳትፎ ያስታውሳታል። የመጽሃፍትን መንደር ለሚያስስም ሰው ማርታ እንግዳ አይደለችም። ማሬ መጽሃፍት በተሰኘ ድርጅቷ በኩል ለአንባቢያ መጽሃፍትን በያሉበት አደርሳለች። አሁን ደግሞ የማህበራዊ መገናኛዎችን በተለይ ደግሞ የዩቱዩብ አውታርን ከሚጎበኙ ኢትዮጵያዊያን ጋር የሚያቀራርባት አዲስ ጥረት ጀምራለች።