ዋሽንግተን ዲሲ —
በተለያዩ የዓለም አቀፍ የዜና ተቋማት ዘጋቢነት ሲንቀሳቀስ የምናየው፣ ኒው ቢዝነስ ኢትዮጵያ የተሰኘው የንግድ ጉዳዮች ዘጋቢ ገፅ መስራች አንዱዓለም ሲሳይ አሻግሮ ማለም ላለው ፋይዳ ምስክር ነው።
ከዐመዴ ገበያ(መርካቶ) ጫማ ሰሪነት ህይወት ተነስቶ፣ የተለያዩ ዓለም ሀገሮችን እንዲዳስስ ዕድሉን ወደ ከፈተለት ሙያ ለመሻገር ያስቻለው -ህልምን ለመኖር የተደረገ ጥረት ፣ አርቆ ዓላሚነት እንደሆነ ያምናልና።
አንዱዓለም በቅርቡ «ህልምህን ኑር!» የተሰኘ ለወጣቶች የህይወት ልምድ የሚያካፍል የዩቲዩብ አውታር ከፍቷል።በዚህ አውታር ላይ ከአነቃቂ ሀሳቦች በተጨማሪ ሙያዊ ምክሮችን ያጋራበታል።
ከሀብታሙ ስዩም ጋር በሚኖራቸው ቆይታ እነኝህን እና ሌሎች ጉዳዮችን አንስተው ተጨዋውተዋል።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ