የኢትዮጵያዊያን “ኔትፍሊክስ ” ለመሆን ተስፋ የሰነቀው “ሀበሻ ቪው”

Habeshaview streaming service

ፊልሞችን፥የኢንተርኔት ላይ ቴሌቭዥኖችን እና የመሳሰሉትን በማሰራጨት ረገድ "ኔትፍሊክስ " እና "አማዞን" የተሰኙት የአሜሪካ ኩባንያዎች ግንባር ቀደም ናቸው።

የእነዚህን ተቋማት አበርክቶት በመከተል ፤ለኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ -ኢትዮጵያዊያን የሚሆኑ መርሃ -ግብሮችን ለማሰራጨት ያቀደ ድርጅቱ በቅርቡ ስራ ጀምሯል።

የድርጅቱ ስም “ሀበሻ ቪው” ሲሆን፤ኑሯቸውን በውጭ ሀገራት ባደረጉ ሶስት ትውልደ -ኢትዮጵያዊያን የተጀመረ አገልግሎት ነው።

ሀብታሙ ስዩም እንግሊዝ ሀገር ከምትገኘው ፥ከድርጅቱ መስራቾች መካከል አንዷ ከሆነችው(የድርጅቱ የስራ ክንውን ሃላፊም ናት) ፤ትዕግስት ከበደ ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል።

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያዊያን «ኔትፍሊክስ » ለመሆን የሰነቀው «ሀበሻ ቪው»