የኢትዮጵያዊያን ስደተኞች የርስበርስ ግጭት በግብጽ

ካይሮ ፣ ግብጽ

በግብጽ በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች መካከል ማንነትን የለየ ግጭት እየተደጋጋመ በመምጣቱ በከፍተኛ ስጋት ጭንቀት ውስጥ ውስጥ እንደሚገኙ በዚያ የሚኖሩ ስደተኞች ለአሜሪካ ድምጽ ተናገሩ።

የኦሮሞ ማህበረሰብ አባላት በሆኑ ወጣቶች ጥቃት ደርሶብናል የሚሉ ሁለት ወጣቶች በስደት በሚኖሩበት ስፍራ ጥቃት ደርሶብናል ሲሉ ተናግረዋል።

በካይሮ የአሮሞ ማህበረሰብ መሪ በበኩላቸው ወጣቶቹ ያቀረቡት ክስ አስተባብለዋል። የአሮሞ ማህበረሰብ አባል የሆኑ ስደተኞች በግብጻዊያን ሳይቀር ጥቃት የሚሰነዘርባቸው ፣እንደሌላው ስደተኛ የሚንገላቱ እንጂ ሌላውን ስደተኛ የሚያጠቁ እንዳልሆነም ይሟገታሉ።

ሀብታሙ ስዩም ዝርዝር ዘገባውን አሰናድቷል።

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያዊያን ስደተኞች የርስበርስ ግጭት በግብጽ