የቀድሞው የአረና ትግራይ ፓርቲ ሊቀመንበር አብርሃ ደስታ ከእስር ተፈቱ

የቀድሞው የአረና ለልዑላዊነት እና ዴሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ አብርሃ ደስታ

ታዋቂው ፖለቲከኛ አብረሃ ደስታ ከእስር መፈታታቸውን ጠበቃቸው ለአሜሪካ ድምጽ ተናገሩ። ቀደም ብለው በአረና ትግራይ የፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ በነበራቸው ሚና እንዲሁም በቅርብ ጊዜ ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ ውስጥ በነበራቸው ተሳትፎ(የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ዋና ኃላፊ ​ሆነው ሰርተዋል) ፣ የትግራይን ክልል የፖለቲካ ሁኔታ በሚመለከት በሚሰነዝሯቸው ሀሳቦች የሚታወቁት አቶ አብርሃ ሁለት ወራትን ከተሻገረ እስር በኃላ የተፈቱት በ10ሺ ብር ዋስትና እንደሆነም ተሰምቷል ።

ሀብታሙ ስዩም የአቶ አብርሃ ጠበቃ ከሆኑት አቶ ተስፋለም በርሄ ጋር ያደረገው አጭር ቆይታ ከስራ ይገኛል ።

Your browser doesn’t support HTML5

የቀድሞው የአረና ፓርቲ ሊቀመንበር አብርሃ ደስታ ከእስር ተፈቱ