ቆይታ ከበጎ አድራጊው ወጣት ዘካሪያስ ኪሮስ ጋር

Your browser doesn’t support HTML5

አዲስ አበባ ጎጃም በረንዳ አካባቢን የሚያዘወትር ሰው ወጣቱን በጎ አድራጊ ዘካሪያስ ኪሮስን ያወቀዋል። ዘካሪያስ እጅ አጥሯቸው ጎዳና የወደቁትን ይመግባል፣ ለአረጋዊያን የንጽህና አገልግሎት ይሰጣል፥ የዘመመ ጎጃቸውን ይጠግናል። እሱ እና አጋሮቹ የሚያደርጓቸውን መልካም ግብሮች በማህበራዊ መገናኛዎች የሚያዩ ኢትዮጵያን የተቻለቸውን ይደግፋሉ። የተገኘውን ይዞ ዘካሪያስ ርዳታ ወደ ሚያስፈልጋቸው ወገኖች ቤት ይመላለሳል።