«ህልምህን ኑር » ፦አጭር ቆይታ ከጋዜጠኛ እና አነቃቂ መርሃ-ግብሮች ፈጣሪው አንዱዓለም ሲሳይ ጋር

አንዱዓለም ሲሳይ የኒው ቢዝነስ ኢትዮጵያ ድረገፅ መስራች ነው።የተለያዩ ዓለም አቀፍ የዜና ተቋማት ዘጋቢም ነው።

በተለያዩ የዓለም አቀፍ የዜና ተቋማት ዘጋቢነት ሲንቀሳቀስ የምናየው፣ ኒው ቢዝነስ ኢትዮጵያ የተሰኘው የንግድ ጉዳዮች ዘጋቢ ገፅ መስራች አንዱዓለም ሲሳይ አሻግሮ ማለም ላለው ፋይዳ ምስክር ነው።

ከዐመዴ ገበያ(መርካቶ) ጫማ ሰሪነት ህይወት ተነስቶ፣ የተለያዩ ዓለም ሀገሮችን እንዲዳስስ ዕድሉን ወደ ከፈተለት ሙያ ለመሻገር ያስቻለው -ህልምን ለመኖር የተደረገ ጥረት ፣ አርቆ ዓላሚነት እንደሆነ ያምናልና።

አንዱዓለም በቅርቡ «ህልምህን ኑር!» የተሰኘ ለወጣቶች የህይወት ልምድ የሚያካፍል የዩቲዩብ አውታር ከፍቷል።በዚህ አውታር ላይ ከአነቃቂ ሀሳቦች በተጨማሪ ሙያዊ ምክሮችን ያጋራበታል።

ሀብታሙ ስዩም ጋር በሚኖራቸው ቆይታ እነኝህን እና ሌሎች ጉዳዮችን አንስተው ተጨዋውተዋል።

Your browser doesn’t support HTML5

«ህልምህን ኑር » ፦አጭር ቆይታ ከጋዜጠኛ እና አነቃቂ መርሃ-ግብሮች ፈጣሪው አንዱዓለም ሲሳይ ጋር