"የተዘረፈውና የተጎዳው" ወልድያ ዩኒቨርሲቲ

ወልድያ ዩኒቨርስቲ

ሰሜን ወሎ አካባቢዎች ውስጥ በህወሓት ተፈፅመዋል የተባሉ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳቶች በስፋት እየተነገሩ ነው።

ከነዚህም ውስጥ አንዱ በሆነው የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ላይ ከስድስት ቢልዮን ብር በላይ የሚገመት ዘረፋና ውድመት እንደደረሰበት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ለቪኦኤ ገልፀዋል።

በዚህም ምክንያት ዩኒቨርሲቲው አሁን የመማር ማስተማር ተግባሩን ለማከናወን የማይችልበት ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ፕሬዚዳንቱ አስታውሰው የሚመለከታቸው አካላት ፈጣን ርብርብ እንዲያደርጉና ዩኒቨርሲቲው መደበኛ ተግባሩን ፈጥኖ መጀመር ማስቻል እንደሚገባ በማሳሰብ ጥሪ አስተላልፈዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ።

Your browser doesn’t support HTML5

"የተዘረፈውና የተጎዳው" ወልድያ ዩኒቨርሲቲ