የዓለም ባንክና አሜሪካ በሶማሌ ክልል ድርቁን ለመቋቋም ድጋፍ ሰጡ

Your browser doesn’t support HTML5

የዓለም ባንክ በሶማሌ ክልል የደረሰውን ድርቅ ለመመከት የሚያስችል የሚውል 63 ሚሊዮን ደላር ወይም ከ3.3 ቢሊዮን ብር በላይ መመደቡን አስታውቋል። ከዚህ ውስጥ ከግማሽ የሚበልጠው ወዲያው እንደሚለቀቅ ገልጿል። የዩናይትድ ስቴትስ የዓለምአቀፍ ልማት ኤጀንሲ /ዩኤስኤአይዲ/ም የድርቁን ጉዳት ለመቀነስ በሚል ተጨማሪ 39 ሚሊዮን ደላር ወይም 2 ቢሊዮን ብር ገደማ እንደሚልክ አመልክቷል።