የትውልደ ኢትዮጵያ መራጮች አስተያየት

Your browser doesn’t support HTML5

ዛሬ፤ ማክሰኞ፣ ጥቅምት 29/2015 ዓ.ም. ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የምርጫ ቀን ነው። አሜሪካዊያን የተወካዮች ምክር ቤቱ በማን አብላጫ መቀመጫ ቁጥር ሥር ሆኖ እንደሚቀጥል ይወስናሉ። ይህ የፕሬዘዳንት ጆ ባይደን የሥልጣን ዘመን አማካይ ጊዜ ምርጫ ነው።

የተወካዮች ምክር ቤቱ የህግ መምሪያ ሁሉም 435 መቀመጫዎች ድምፅ ይሰጥባቸዋል። መቶ መቀመጫ ባለው የህግ መወሰኛ 35 ወንበሮች ለሽሚያው ክፍት ናቸው፤ ዛሬ ይሞላሉ።

ትውልደ ኢትዮጵያ አሜሪካውያንም በዚህ ምርጫ ተሳታፊ ናቸው። መራጮችም አስመራጮችም ይሆናል። ከኖርዝ ካሮላይና ሻርለትና ከአትላንታ አስተያየት ጠይቀናል።

/አስተያየቱን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/