በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዙርያ በሚነሱ ጥያቄዎች ላይ የገንዘብ ሚንስትር ድኤታ የሰጡት ምላሽ ክፍል -1

Your browser doesn’t support HTML5

የውጭ ምንዛሬ በገበያ ዋጋ እንዲወሰን የሚያደርገው የኢኮኖሚ ማሻሽያ በአይ ኤም ኤፍ አስግዳጅነት የተተገበረ ሳይሆን፤ መንግስት የኢኮኖሚ ችግሮችን ለመፍታት የተገበረው ነው” ሲሉ የገንዘብ ሚንስትር ድኤታ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ከአሜሪካ ድምጽ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት የተለያዩ ድጎማዎችን በማድረግና የደሞዝ ማሻሽያ በማድረግ ማሻሽያውን ተከትሎ ያለውን የኑሮ ውድነት ለማረጋጋት እየሰራ ነው ይላሉ፡፡ የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት የሚውል ከ200 ቢሊየን ብር በላይ ተጨማሪ በጀትም ለማስጸደቅ የፖርላማውን ስራ መጀመር በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡