የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ስብሰባ

Your browser doesn’t support HTML5

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዥ እና የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ረቡዕ እለት በዩናይትድ ስቴትስ ኒው ዮርክ በሚገኘው የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ቢሮ በአምስተኛው የአፍርካ ሕብረት እና የመንግስታቱ ድርጅት ስብሰባ ላይ ተገኝተዋል፡፡ የመንግስታቱ ድርጅት እና የአፍሪካ ሕብረት በሰላም እና ጸጥታ ዙሪያ ሊኖራቸው ስለሚገባው የላቀ ትብብር እና አጀንዳ 2063 እና አጀንዳ 2030 ተብለው በሚታወቁት የዘላቂ ልማት ጉዳዮች ላይም ተወያይተዋል፡፡