የሶማሊያ ድርቅ ቸነፈር ከመሆን በጥቂቱ ነው የዳነው ሲል የመንግስታቱ ድርጅት አስታወቀ

Your browser doesn’t support HTML5

ተመድ በትላንትናው ዕለት የሶማሊያውን ረሃብ አስመልክቶ ባወጣው ዘገባ እንዳመለከተው የረድኤት ድርጅቶች እና የአካባቢው ማኅበረሰቦች ሰብዓዊ ቀውሱን ለመቋቋም ባደረጉት ጥረት የቸነፈር አደጋን ለጥቂት ማስወገድ ተችሏል። የተ.መ.ድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ቃል አቀባይ የንስ ላርከ በሰጡት አስተያየት የሰብአዊ ቀውሱን ያመጣው ሁኔታ አልተቀየረም። ድርቁ ወደ ቸነፈር ሊሸጋገር የመቻሉ ስጋት አሁንም አለ ሲሉ አስጠንቅቀዋል። /ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/