ምግብን እንደ መድኃኒት

Your browser doesn’t support HTML5

የዘመናዊ ሕክምና አባት እየተባለ የሚጠራው ሂፖክራተስ፣ “ምግብ መድኃኒት፤ መድኃኒትም ምግብ ይኹን” በተሰኘው ብሂሉ ይታወቃል። ከኹሉ በላይ አባባሉ፣ ምግብ፥ ሰዎች ጤናቸውን ከበሽታ ለመጠበቅ፣ ሲቃወስም ለማስተካከል ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ ጠቋሚ ነው። የጤና ታዛቢዎች፥ በዓለም ላይ “አመጋገብን በማስተካከል ጤናን መጠበቅ” የሚለው ሐሳብ ተቀባይነቱ እየጨመረ እንደመጣ ያመለክታሉ፡፡ /ይህን እና ሌሎች የኑሮ በጤንነት ዘገባዎች ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/