ስጋት ላይ የወደቀው የእናቶች እና የሴቶች ጤና አገልግሎት አቅርቦት

Your browser doesn’t support HTML5

የዋይት ኃውስ ድረ ገጽ ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያመላከተው፤ በጎርጎርሳውያኑ 2022 ዩናይትድ ስቴትስ በአፍሪካ 11.5 ቢሊየን ዶላር ለኤች አይቪ ኤድስ ድጋፍ እንዲሁም ሁለት ቢሊየን ዶላር ደግሞ ለቤተሰብ ምጣኔና፣ ለስነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት አቅርቦቶች እንዲሁም ለእናቶች እና ጨቅላ ህጻንት ጤና ላይ ፈሰስ እንደምታደርግ አስታውቋል።

47ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሀገር ውስጥ የጽንስ ማቋረጥ ላይ ያላቸው አቋም፣ በአለም አቀፍ ደረጃ ዩናይትድ ስቴትስ ለጽንስ ማቋረጥ እና ለስነ ተዋልዶ የምታደርገውን ድጋፍ እንዳያስተጓጉል ስጋት አስከትሏል። ኤደን ገረመው ባለሞያዎችን አነጋግራ ያሰናዳቸው ዘገባ በዚህ ዙሪያ ያተኩራል።