ኢትዮጵያዊው ከ30 የዓለም "የሕዋ መሪ ወጣቶች" መሃከል አንዱ ኾኖ ተመረጠ

Your browser doesn’t support HTML5

በቅርቡ ከመቐለ ዩኒቨርስቲ በመካኒካል ምሕንድስና የተመረቀው ትንሣኤ ዓለማየሁ፣ ባሳለፍነው ሳምንት በዓለም አቀፉ የጠፈር ምርምር ፌዴሬሽን ተስፋ ከተጣለባቸው 30 "የሕዋ መሪ ወጣቶች" መሃከል አንዱ ኾኖ ተመርጧል፡፡

ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ወቅት፣ በአፍሪካ የሕዋ ኢንዱስትሪ፣ ከ30 ዓመት በታች ያሉ ዐሥር ወጣቶች መሃከል አንዱ ኾኖ የተመረጠው ትንሣኤ፣ የስፔስ ጄኔሬሽን ም/ቤት የአፍሪካ ቀጣናዊ አስተባባሪ ኾኖ እያገለገለ ይገኛል፡፡

ከጋቢና ቪኦኤ ጋራ በነበረው ቆይታ “ገና ብዙ የሚቀረን ነገር አለ” ያለው ትንሣኤ ዓለማየሁ “ምርጫውን ጥሩ መስመር ላይ ናችሁ በሚል ነው የተረዳኹት” ብሎናል።

/ሙሉ ዘገባውን ከተያይዘው ፋይል ይከታተሉ/