“እንደ ሃገር አንድ አስቻይ ሁኔታ ፈጥረናል" የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ

Your browser doesn’t support HTML5

በቅርቡ ኢትዮ ቴሌኮም ያስጀመረው የ5ኛ ደረጃ የሞባይል ቴክኖሎጂ አገልግሎት (5G) የተለያዩ ድርጅቶችን፣ ተቋማትንና በኢንዱስትሪው ዘርፍ የተሰማሩ ኩባንያዎችን ምርታማነትና ውጤታማነትን እንደሚያሻሽል ተገለፀ፡፡ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ይህ ቴክኖሎጂ በኢንተርኔት ከፍተኛ ባንድዊድዝ የሚፈልጉ ስራዎችን ለማከናወን የሚያስችል በመሆኑ በሀገር ደረጃ ትልቅ ኢኮኖሚያዊ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል፡፡