በደላንታ ወረዳ ዋሻ የተናደባቸውን የኦፓል አምራቾች ለመታደግ ጥረቱ ቀጥሏል

Your browser doesn’t support HTML5

በክልሉ ደቡብ ወሎ ዞን በኦፓል ማዕድን ሀብቷ በምትታወቀው ደላንታ ወረዳ በባህላዊ መንገድ የኦፓል ማዕድን የሚያመርቱ ወጣቶች፣ ኀሙስ ጥር 30 /2016 ዓ.ም. እኩለ ሌሊት ገደማ ዋሻ ውስጥ በቁፋሮ ላይ እያሉ በግዙፍ ናዳ በመያዛቸው ሕይወታቸውን ለመታደግ ጥረት እየተደረገ እንደሆነ የወረዳው አስተዳደር ገለጸ፡፡