የጡት ካንሰርን ማሸነፍ ቆይታ ከበሽታው ካገገሙት ዶ/ር ፍሬሕይወት ደርሶ ጋር

Your browser doesn’t support HTML5

ወርሃ ጥቅምት የአለም አቀፉ የጡት ካንሰር ግንዛቤ ማስጨበጫ ወር በመባል ይታወቃል። በአለም ላይ ከስምንት ሴቶች አንዷ በጡት ካንሰር እንደምትያዝ በዩናይትድ ስቴትስ በካንሰር ዙሪያ የሚሰራው ገባሬ ሰናዩ የአሜሪካ የካንሰር ማኅበረሰብ አማካኝነት የተሰሩ ጥናቶች ያመላክታሉ። በኢትዮጵያም በበሽታው ዙሪያ ያለው ግንዛቤ እና እንዲሁም የህክምናው ተደራሽነት አነስተኛ መሆኑን ታካሚዎች እና የጤና ባለሞያዎች ይናገራሉ።

ኤደን ገረመው የጡትካንሰር ታማሚ የነበሩትን እና ቀድሞ ዐለም ጸሃይ ፋውንዴሽን በመባል ይታወቅ የነበረው የአሁኑን ዐለም ፍሬ ፒንክ ሀውስ ካንሰር ፋውንዴሽን መሥራች እና ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ፍሬ ሕይወት ደርሶን አነጋግራለች፡፡ ስለተሞክሯቸው እና ተቋማቸው ለካንሰርህሙማን እና ቤተሰቦቻቸው ስለሚያደርገው ድጋፍ እና እንቅስቃሴ አውግተዋታል።