በምጣኔ ሀብታዊ እና ሰብአዊ መርሀ ግብሮች የሚሳተፉት የምክር ቤት አባል

Your browser doesn’t support HTML5

አቶ ከማል ሀሺ የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር አባል ሲኾኑ፣ በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በሚያሳትፉ ምጣኔ ሀብታዊ እና ሰብአዊ መርሀ ግብሮችን ያስተባብራሉ።

በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዘርፈ ብዙ ተሳትፎ እርሳቸው የወከሉትን የሶማሌ ክልል አራቢ ምርጫ ክልል መራጮችና ለተቀረውም የሀገሪቱ ሕዝብ የላቀ ዋጋ እንዳለው የሚናገሩት አቶ ከማል፣ ከመረዳዳት የተሻገረ የጋራ ተጠቃሚነት ሊዳብር እንደሚገባም ይመክራሉ። ሰሞኑን ዋሽንግተን ዲሲ ብቅ ያሉትን የሕዝብ እንደራሴ በአሜሪካ ድምጽ ስቱዲዮ አነጋግረናቸዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።