የኢትዮጵያ ሰላም ድርድር እና የወጣቶች ጥያቄ

Your browser doesn’t support HTML5

ሁለት ዓመት ሊሞላው የቀናት እድሜ ብቻ በቀሩት የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት የተነሳ ብዙ ንጹሃን ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል፣ ተፈናቅለዋል እንዲሁም ቤት እና ንበረታቸውን ማጣት ጨምሮ ለብዙ ዓይነት የጦርነት ወንጀሎች ተጋልጠዋል። ጦርነቱ ካስከተለው ሰብዓዊ ቀውስ በተጨማሪም በምጣኔ ሃብቱ ላይ እጅግ ብዙ ጫናዎችን ያመጣ ሲሆን ከስልሳ በመቶ በላይ የሚሆነው ህዝቧ ወጣት ለሆነችው ሃገር ወጣቶች ተስፋ በመቁረጥ፣ በስራ አጥነት ጨምሮ እጅግ ብዙ ተግዳሮችን እያሳለፉ ይገኛሉ።

ሃገሪቱ ወደ ቀደመ ሰላሟ ትመለስ ዘንድ የኢትዮጵያ መንግስት እና ሕወሃት ለመጀመሪያ ጊዜ ለሰላም ድርድር በደቡብ አፍሪካ ተገናኝተው ውይይት ጀምረዋል። ለመሆኑ ወጣቶች ከዚህ ድርድር ምን ይጠብቃሉ?

/ዝርዝሩን ከተያያዘው የምስል ፋይል ይከታተሉ/