የቤት ውስጥ ጭስ እና የጨቅላ ሕጻናት የመተንፈሻ ችግር

Your browser doesn’t support HTML5

ኢትዮጵያ ውስጥ የሕጻናት ህይወት ከሚቀጥፉ እና ለድንገተኛ ሞት ከሚዳርጉ በሽታዎች አንዱ የመተንፈሻ አካላት ችግር ነው። በመኖሪያ ቤቶች ውስጥ የሚነዱ ከእንጨትና ከከሰል የሚወጡ ጭሶች እንዲሁም ደግሞ ከጊዜ ወደ ጊዜ በከተሞች እየተለመደ የመጣው በቤት ውስጥ ሺሻ የማጨስ ልማድ በሕጻናት በተለይም በጨቅላ ህጻናት ሕይወት ላይ ከፍተኛ አደጋ ጋርጧል ይላሉ በጅማ ዩኒቨርስቲ ውስጥ የህጻናት ሃኪም የሆኑት ዶ/ር መሃመድ በሽር። /ዝርዝሩን ከተያያዘው የምስል ፋይል ይከታተሉ/