አካል ጉዳተኛው በኪነጥበብ ውስጥ ቦታ እንዲያገኝ የሚሰራው ካቲም ተቋም

Your browser doesn’t support HTML5

ካቲም የዳንስ ቡድን ከአምስት ዓመት በፊት በአማኑኤል ሰለሞን እና አብረውት በዳንስ ይሳተፉ በነበሩ ሌሎች አካል ጉዳተኛ ጓደኞቹ አማካኝነት የተመሰረተ ተቋም ነው። ተቋሙ ሙሉ ለሙሉ በአካል ጉዳተኞች የተመሰረተ ቢሆንም ዘመናዊ እና ባህላዊ የዳንስ ስልጠናዎችን ለአካል ጉዳተኞች እና ለጉዳት አልባዎች ይሰጣል።

ላለፉት ሥስት ዓመታት በተከታታይ እንችላለን የተሰኘ ዓመታዊ ፌስቲቫል ሲያዘጋጅ የቆየ ሲሆን ዘንድሮም በአዲስ አበባ ከተለያዩ ክፍለ ከተማዎች ከ 1 እስከ 3 ለወጡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች፣ ለረዥም ጊዜ ያገለገሉ አካል ጉዳተኛ መምህራን እና እንዲሁም በተለያዩ የስራ ዘርፎች ስኬታማ ለሆኑ ግለሰቦችን ለመሸለም ተዘጋጅቷል።

/ዝርዝሩን ከተያያዘው የምስል ፋይል ይከታተሉ/