ባይደን  ምክር ቤቱን ለዩክሬን የ33 ቢሊዮን ዶላር እርዳታ ጠየቁ 

Your browser doesn’t support HTML5

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ትናንት ሐሙስ የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት ለዩክሬን ደህንነትና የሰብአዊ ድጋፍ የሚውል 33 ቢሊዮን ዶላር ተጨማሪ እርዳታ እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡ የባይደን ጥያቄ የመጣው ህግ አውጭዎቹ የምክር ቤት አባላት፣ ያለንምንም በቂ ምክንያት የተካሄደውን የሩሲያን ወረራ ለመመከት የሚውል፣ የጦር መሳሪያ በአፋጣኝ እንዲሰጥ፣ ውሳኔያቸውን ባስተላለፉትበት ወቅት ነው፡፡