ከሩሲያ እስር የተለቀቁት አሜሪካውያን ከቤተሰቦቻቸው ተቀላቅለዋል 

Your browser doesn’t support HTML5

ከሩሲያ እስር የተለቀቁት አሜሪካውያን፣ ትላንት ኀሙስ ምሽት፣ ዩናይትድ ስቴትስ የገቡ ሲኾን፣ ፕሬዚዳንት ባይደንና ቤተሰቦቻቸው የደስታ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

አሜሪካውያኑን ጨምሮ በጠቅላላው በሩሲያ ታግተው የቆዩ 16 እስረኞችን ለመለቀቅ ያበቃው የእስረኛ ልውውጥ ስምምነት፣ በብዙ አጋሮች ትብብር እና ብርቱ የዲፕሎማሲ ጥረት የተገኘ እንደኾነ ተመልክቷል።