የስደተኛውን ማኅበረሰብ ጤና የሚከባከበው የኮሎራዶው ልዩ ክሊኒክ

Your browser doesn’t support HTML5

በዩናይትድ ስቴትሷ የኮሎራዶ ክፍለ ግዛት ውስጥ የሚኖሩ የስደተኛ ማኅበረሰብ አባላት፣ ሕመም በተሰማቸው ጊዜ የሕክምና ርዳታ ፍለጋ የሚያቀኑበት ልዩ ሥፍራ አለ፡፡ የኮሎራዶ ልዩ ክሊኒክ፣ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ከመጡ ብዙ ጊዜ ያልኾናቸው የልዩ ልዩ ሀገራት ተወላጅ ስደተኞችን የሚያገለግል የጤና ክብካቤ ክሊኒክ ነው።

Svitlana Prystynska ለአሜሪካ ድምፅ ያጠናቀረችው ዘገባ፣ በአንድ ወቅት ከዩክሬን ተሰድደው በመጡ አንዲት የሕክምና ባለሞያ ስለተቋቋመው ስለዚኽ የሕክምና ክሊኒክ ይተርካል።