በኢትዮጵያ ለስድስት ሚሊዮን ሰዎች የኤችኣይቪ ምርመራ ለማካሄድ ያለመ ዘመቻ ይፋ ሆነ

  • እስክንድር ፍሬው
በሚቀጥሉት ሦስት ወራት ብቻ ለስድስት ሚሊዮን ሰዎች የኤችኣይቪ ምርመራ ለማካሄድ ያለመ ዘመቻ ዛሬ በኢትዮጵያ ይፋ ተደርጓል።

ከአሜሪካ ኤምባሲ የተሰራጨው መረጃ እንደሚያሳየው የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥትና አለምአቀፍ ተቋማት ለዚህ ዘመቻ ድጋፍ ያደርጋሉ።

የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ትላንት ባሰራጨው መግለጫ እንደሚያመለክተው ዘመቻው 909090 የተሰኘውን ግብ ለማሟላት ያለመ ነው። የኤድስን ጉዳይ በሚከታተለው የተባበሩት መንግሥታት ተቋም የተቀረጸው ይህ ግብ ምን ማለት እንደሆነም መግለጫው ጠቁሟል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ ለስድስት ሚሊዮን ሰዎች የኤችኣይቪ ምርመራ ለማካሄድ ያለመ ዘመቻ ይፋ ሆነ