የህንድና የዩናይትድ ስቴትስ የንግድ ግንኙነት

  • ቪኦኤ ዜና

የዩናይትድ ስቴትስ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ

ከህንድ ጋር ጥብቅ የሆነ ግንኙነት እንደሚፈጠር የተናገሩት የዩናይትድ ስቴትስ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ፣ ሁለቱ ሀገሮች፣ በወዳጅነት መንፈስ፣ ልዩነቶቻቸውን በንግድና በሌሎች ጉዳዮች እንደሚፈቱ ተስፋችውን ገልፀዋል።

የአሜሪካው ከፍተኛ ዲፕሎማት፣ ከህንዱ አቻቸው ኤስ ጃይ ሻን ካር እና ከህንዱ ጠ/ር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ዛሬ ረቡዕ በተገናኙበት ወቅት ነው ይህን ያስታወቁት።

ጠ/ሚኒስትር ሞዲ ድጋሜ ከተመረጡ ወዲህ፣ የሁለቱ ሀገሮች ከፍተኛ ባለሥልጣናት ሲገናኙ ይሄ የመጀመሪያ መሆኑ ነው።