የአፍሪካ-ዩናይትድ ስቴትስ መሪዎች ስብሰባ ዋሺንግተን ላይ ተጀመረ

  • ቪኦኤ ዜና

የአፍሪካ-ዩናይትድ ስቴትስ መሪዎች ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ የአጎአን ጉባዔ ሲከፍቱ

መንግሥታት ክፍት የሆነና ሲቪል ማኅበረሰቡን ያሣተፈ አሠራር በመከተላቸው ምክንያት የሚያተርፉት ተዓማኒነትን፤ ውጤቴማነትንና ሙስናን መዋጋትን እንደሆነ ዋሺንግተን ዲሲ ላይ በተየመረው የአፍሪካ መሪዎች ጉባዔ ላይ ተነግሯል፡፡

የክፍት መንግሥታዊ አሠራር አጋርነት መድረክ ሲቪል ማኅበረሰቡን ይበልጥ ውጤታማ በሆነ መንገድ ማጠናከር የሚቻልባቸውንም መንገዶች አንስቷል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የፀጥታና የግልፅነት፣ ጉዳዮች ሲቪል ማኅበረሰቦችና የፖለቲካ እንቅስቃሴ፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ተቋማትና የለጋሾቻቸው ፍላጎቶችን የሚመለከቱ አስተያየቶች ተንፀባርቀዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡