ታዛቢዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ተጠየቀ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ጉዳዮች ከፍተኛ ኮሚሽነር ዛይድ ራዓድ አልሁሴን

ኢትዮጵያ ውስጥ ተቃውሞ በተካሄዱባቸው አካባቢዎች ዓለምአቀፍ ገለልተኛ ታዛቢዎች እንዲገቡና እንዲመለከቱ መንግሥቱ እንዲፈቅድ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጥሪ አቀረበ።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ጉዳዮች ከፍተኛ ኮሚሽነር ዛይድ ራዓድ አልሁሴን ኢትዮጵያ ውስጥ የተቃውሞ ሰልፎች በተካሄዱባቸው አካባቢዎች ዓለምአቀፍ ታዛቢዎች ገብተው እንዲመለከቱ መንግሥት እንዲፈቅድ ጥሪ አቅርበዋል።

ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ቡድን ሂዩማን ራይትስ ዋች ደግሞ ለዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንትነት የሚወዳደሩት ዕጩዎች በአሜሪካና በተቀረውም ዓለም ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ ለማድረግ ያላቸውን አቋም ግልፅ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

Your browser doesn’t support HTML5

ታዛቢዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ የተባበሩት መንግሥታት ከፍተኛ ኮሚሽነር ጠየቁ

ተወዳዳሪዎቹ ፕሬዚዳንት ሆነው ከተመረጡ ዋና ዋና የሚባሉ የሰብዓዊ መብቶች ጥያቄዎችን እንዴት እንደሚመለከቱ ለማወቅ የመብቶች ተሟጋቹ ቡድን 12 ጥያቄዎችን አቅርቧል።

“ሰብዓዊ መብቶችን ከሚረግጡት ሀገሮች አንዷ ኢትዮጵያ ናት” ብሏል ሂዩማን ራይትስ ዎች።

Your browser doesn’t support HTML5

ታዛቢዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ተጠየቀ