ትግራይ ክልል ሰብዓዊ እርዳታ ለማድረስ እንዲቻል ተመድ በድጋሚ ጠየቀ

Your browser doesn’t support HTML5

ትግራይ ክልል ውስጥ ለሲቪሎች ሰብዓዊ እርዳታ ማድረስ እንዲቻል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በድጋሚ መጠየቁ ተዘግቧል።  ከአንድ ወር በላይ በዘለቀው ውጊያ ምክንያት በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ በግጭት አካባቢዎች የሚኖሩ ሰዎች የለት ደራሽ እርዳታ ፈላጊ መሆናቸውም ተገልጿል።