የተበተኑትን ኤርትራዊያን ስደተኞች ለማሰባሰብ እየጣረ መሆኑን ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አገልግሎት አስታወቀ

Your browser doesn’t support HTML5

በአፋር ክልል በርሃሌ ከሚገኘው የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ኤርትራውያን የተፈናቀሉት በህወሓት ምክኒያት መሆኑን የኢትዮጵያ ስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አገልግሎት አስታወቀ።

በመጠለያ ጣቢያ ውስጥ የነበሩት በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ወደ ሰመራና ሌሎች አካባቢዎች ለመፈናቀል መገደዳቸውንም የአገልግሎቱ የኮሙኒኬሽንና የውጭ ግንኙነት ዳይሬክተሩን በአካል ንጉሴን ተናግረዋል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኛ ጉዳዮች ከፍተኛ ኮሚሽነር /ዩኤንኤችሲአር/ ጥቃቱ በታጣቂዎች መፈፀሙንና ስደተኞቹ መፈናቀላቸውን እንጂ ድርጊቱ በማን እንደተፈፀመ እንደማይታወቅ አስታውቋል።