ከዩክሬን እህል የጫነ መርከብ ለኢትዮጵያ እንደሚያደርስ ተገለፀ

Your browser doesn’t support HTML5

ከዩክሬን ኦዴሳ ወደብ የተነሳ ሁለት መቶ ሰላሣ ሺህ ኲንታል ስንዴ መድረሻው ኢትዮጵያ መሆኗ ተነግሯል።

የእርዳታ ነው የተባለው እህል በጅቡቲ ወደብ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገባ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታውቋል።

ከዩክሬን የሚጓጓዘው ስንዴ ድርቅ ወደጎዳቸው ሌሎች ሃገሮችም በዓለም የምግብ ፕሮግራም አማካኝነት እንደሚላክ ተገልጿል።

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ስንዴ ከውጭ ልታስገባ መሆኑ በተለያዩ የማኅበራዊ መገናኛዎች ላይ ቢነገርም ከዩክሬን ስንዴ አለመግዛቱን መንግሥቷ አስታውቋል።