ከሠላሳ ሺህ በላይ የኮንጎ ስደተኞች በጀልባ ኡጋንዳ ገብተዋል

Your browser doesn’t support HTML5

ካለፈው ጥር ወር አንስቶ ከሠልሳ ሺህ በላይ የሚሆኑ የኮንጎ ስደተኞች በደካማ ጀልባዎች ኡጋንድ ገብተዋል። በሰሜን ምሥራቅ የኮንጎ ዲሞክራስያዊ ሪፖብሊክ ከሚካሄደው የኅብረተሰቦች ግጭት ለመሸሽ ነው የሚሰደዱት። በኮንጎ ዲሞክራስያዊ ሪፖብሊክና በደቡብ ሱዳን በሚካሄደው ግጭት ምክንያት ኡጋንዳ የተጠለሉት የሰደተኞች ብዛት ከ1.4 ሚልዮን በላይ ደርሷል፣ ቁጥሩ እየጨመረ መሄዱም ተገልጿል።