ህወሓት ከሃገራዊው ገዥ ፓርቲ ራሱን አገለለ
Your browser doesn’t support HTML5
ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ /ህወሓት/ ከሃገራዊው ገዥ ፓርቲ እራሱን አግልሏል።
ብልፅግና ፓርቲን በህገወጥነት የፈረጀው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ /ህወሓት/ ለሁለት ቀናት የጠራውን አስቸኳይ ጉባዔ ትናንት ማምሻውን ሲያጠናቅቅ ባወጣው የአቋም መግለጫ ከፓርቲው ጋር እንደማይወሃድ አስታውቋል።
ከኢህአዴግ ጋር የነበረውን ሃብትና ንብረት የማከፋፈል ሂደት በሕጋዊ መንገድ እንደሚፈፅም ገልጿል።