የአንበጣ መንጋ በትግራይ ክልል

Your browser doesn’t support HTML5

የአንበጣ መንጋ ከትናንት በስትያ ጀምሮ በትግራይ ክልል ሦስት ወረዳዎች መከሰቱን የክልሉ ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ አስታውቋል። የአምበጣ መንጋው እስከ አሁን በተወሰነ የጤፍ አዝርዕት ላይ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን የጉዳት መጠኑ እየተጠና ነው ተብሏል።