በትግራይ ክልል 60ሺሕ ተማሪዎች የስምንተኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናን በመውሰድ ላይ ናቸው

Your browser doesn’t support HTML5

በትግራይ ክልል፣ ከአራት ዓመታት በኋላ፣ ዛሬ ረቡዕ፣ ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. የስምንተኛ ክፍል መልቀቂያ ክልላዊ ፈተና መስጠት ተጀምሯል፡፡

ወደ ፈተና መቅረብ ከሚገባቸው 124 ሺሕ ተማሪዎች ውስጥ፣ ፈተናውን በመውሰድ ላይ የሚገኙት፣ 60 ሺሕ ተማሪዎች ናቸው፤ ብሏል የክልሉ ቢሮ፡፡

የተፈታኝ ቁጥር የቀነሰበት ምክንያት፥ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የማይቆጣጠራቸው ትምህርት ቤቶች መኖራቸው፣ ተማሪዎች መፈናቀላቸው፣ እንዲሁም ጦርነቱ በፈጠረው ኢኮኖሚያዊ ችግር፣ ከግማሽ በላይ ተማሪዎች ወደ ፈተና አልቀረቡም፤ ብሏል ቢሮው፡፡ ዘንድሮ እየተፈኑ የሚገኙት ተማሪዎች፣ በ2012 ዓ.ም. ለመፈተን ተመዝግበው የነበሩ ናቸው፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።