የጦር መሳሪያ ርክክብ በአጉላ

Your browser doesn’t support HTML5

የትግራይ ኃይሎች ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የጦር መሳሪያዎች ማስረከብ መጀመራቸው ተገለፀ። የሰላም ሥምምነቱን ተግባራዊነት የሚከታተልና የሚቆጣጠረው ቡድን ከባድ የጦር መሳሪያዎች ርክክብ መጀመራቸውን መታዘቡን ገልጿል።

ርክክቡ ትናንት ከመቀሌ ከተማ ሰሜን አቅጣጫ 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኝ አጉላ በምትባል አካባቢ መጀመሩን ሁለቱም ወገኖች አረጋግጠዋል።

/ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/