በቴክኖሎጂ ሙያ ራሷን ያወጣች ኢትዮጵያዊት

Your browser doesn’t support HTML5

በቴክኖሎጂ ሙያ ላይ የሚሰማሩ ሴቶች ቁጥር ከወንዶቹ ጋር ሲነፃፀር 26 በመቶ ብቻ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ጥቁር ሴቶች 3 በመቶ ብቻ ናቸው። የዛሬዋ እንግዳችን እሴተ ስዩም ግን እጅግ በጣም ትንሽ ጥቁር ሴቶች በሚገኙበት በዚህ የሙያ ዘርፍ ውስጥ እራሷን አሳድጋ በአለማችን ግዙፍ ከሚባሉት የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች መሀከል፣ ማይክሮሶፍት ካምፓኒ ውስጥ በአመራርነት ታገለግላለች። ባልደረባችን ስመኝሽ የቆየ ከእሴተ ጋር ቆይታ አርጋለች።