ተፈናቃዮች መጠለያ ያደረጓት የሰሜን ዳርፉር ዋና ከተማ ኤል ፋሽር “የለየለት ጦርነት ቀጣና” ሆናለች

Your browser doesn’t support HTML5

በሱዳን ሰሜን ዳርፉር ክፍለ ግዛት የፈጥኖ ደራሽ ድጋፍ ሰጪ ኅይሎች ታጣቂዎች በዋና ከተማዋ ኤል ፋሽር ሆስፒታሎች እና መጠለያ ካምፖች ላይ ጥቃት እያደረሱ መሆኑን ተፈናቃዮች እና ሐኪሞች ተናገሩ፡፡

ግብረ ሰናይ ድርጅቶችም በሱዳኑ ጦርነት ምክንያት ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ ስደተኞች መሸሻ የሆነችው ኤል ፋሽር ስትታመስ ዓለም በቂ ትኩረት አልሰጣትም በማለት ወቅሰዋል፡፡

ሄንሪ ዊልክንስ ከለንደን ያጠናቀረው ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።