ስፔን 629 ፍልሰተኞችን ያሳፈረው መርከብ በወደቧ እንዲያርፍ ፈቀደች

Your browser doesn’t support HTML5

ስፔን 629 ፍልሰተኞችን ያሳፈረው መርከብ ቫሌንሺያ በተባለችው የወደብ ከተማ እንዲያርፍ እንደምትፈቅድ ትላንት አስታውቃለች። አኳርየስ የተባለው ፍልሰተኞቹን ለማዳን ሲል ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ በጀልባ የሊብያ የባህር ጠረፍ ሲደርሱ ያሳፈራቸው መርከብ በዓለምቀፍ ባህሮች ሲንቀሳቀስ ቆይቷል። ማልታና ኢጣልያ በግዛታቸው ያሉትን ስደተኞችና ፍልሰተኞችን እንኳን ማቋቋም አልቻልንም በማለት መርከቡ በወደቦቻቸው እንዲያርፍ አልፈቀዱም።