የደቡብ ሱዳን ሚኒስትር ለቀቁ

  • እስክንድር ፍሬው

የደቡብ ሱዳን የእርሻና የተፈጥሮ ኃብት ሚኒስትር ዶ/ር ላም አኮል

የደቡብ ሱዳን የእርሻና የተፈጥሮ ኃብት ሚኒስትር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት እና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ዶ/ር ላም አኮል ሥልጣናቸውን መልቀቃቸውን አስታውቀዋል።

ምክንያታቸው ፕሬዚዳንት ሳልቫ-ኪር ማያርዲት የሰላም ስምምነቱን ፍቀውታል የሚል እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ዶ/ር ላም አኮል ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃል ደቡብ ሱዳን ውስጥ ተግባራዊ የሚደረግ የሰላም ስምምነት የለም ብለዋል።

ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በበኩሉ የደቡብ ሱዳን ወገኖች ወደ ድርድር እንዲመለሱ እየጎተጎተ ነው፡፡

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

የደቡብ ሱዳን ሚኒስትር ለቀቁ