ድርቅ ትምህርት አደናቀፈ

Your browser doesn’t support HTML5

በደቡብ ክልል በተከሰተ ድርቅ ምክንያት የህፃናት ትምህርት እየተስተጓጎለ መሆኑ ተገልጿል።

ኮንሶ ዞን ውስጥ ብቻ ከ13ሺህ በላይ የሚሆኑ ልጆች ትምህርት ማቋረጣቸውን የዞኑ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር አስተባባሪና የግብርና ኃላፊ አቶ ከፈነ ቲቻሮ ተናግረዋል።

ከነዚህ ውስጥ ግን 5ሺህ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም በመካተታቸው ወደ ትምህርት መመለሳቸውን ገልፀዋል።

270ሺህ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ምገባ እየተደገፉ መሆናቸውን የክልሉ የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬ ተናግረው በድርቁ ምክንያት ስንት ተማሪ እንደተደናቀፈ በውል እንደማያውቁ ገልፀዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ዘገባ ያገኛሉ።