ድርቅ የጎዳው ሶማሌ ክልል

Your browser doesn’t support HTML5

በሶማሌ ክልል በቀጠለው ድርቅ ምክኒያት የእንስሳት ሞት መጨመሩን ክልሉ አስታወቀ። አንዳንድ አካባቢዎች የበልግ ዝናብ ቢያገኙም ለአራተኛ ዓመት የቀጠለው የድርቅ ሁኔታ ባለመቀረፉ በተለይም በሦስት ዞኖች እንስሳት እየሞቱ መሆኑን ጨምሮ ገልጿል።

ድርቁ ከበረታባቸው ዞኖች አንዱ በሆነው ዳዋ ዞን ብቻ ከአንድ ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውና ከ300ሺ በላይ የቁም እንስሳት መሞታቸውን ክልሉ አስታውቋል።

የዳዋ ዞን ነዋሪዎች ከችግሩ ስፋት አንጻር በቂ ድጋፍ እየተደረገላቸው እንዳልሆነ ጠቁመዋል። የሚችሉትን ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን የገለጸው የሶማሌ ክልል አቅም ያላቸው ሁሉ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።