ማህበራዊ የትስስር ገጾችና ግብረ ገብነት 

Your browser doesn’t support HTML5

በማህበራዊ የትስስር ገጾች ላይ በሚተላለፉ መልዕክቶች ጾታን ፣ ሃይማኖትን ወይም ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ስለመበራከታቸውም ተጠቃሚዎችና በዘርፉ ላይ የሚሰሩ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ በማህበራዊ ሚድያዎች የሚተላለፉ ይዘቶች የሃይማኖት ተቋማትንም እንዳሳሰባቸው የወቅቱ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሓፊ የሆኑት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል፡፡