በመንገድ ሥራ ምክንያት ማሳቸው ላይ የተቆለለ አሸዋና ጠጠር ለችግር እንደዳረጋቸው ገበሬዎች ገለጹ

Your browser doesn’t support HTML5

በደቡብ ክልል፥ በጋሞ ጋፋ ዞን፥ የደምባ ጎፋ ወረዳ የሱካና የጉራደ ቀበሌ የሚኖሩ 38 አርሶ አደሮች በመሬት ግንባታ ምክኒያት የእርሻ መሬታቸው ካመረቱት ሰብል ጋር መውደሙን፣ መሬቱ ላይ አሸዋና ጠጠር ተቆልሎ አራት ዓመታት መቆጠሩን አርሶ አደሮቾ ይናገራሉ። ከዚህ በኋላ ማረስ እንዳልቻሉ፣ ልጆቻቸውን ማስተማርና ቤተሰቦቻቸውን መመገብ እንደተሳናቸውም በምሬት ይናገራሉ።